የጽ/ቤቱ ሥልጣንና ተግባር

  1. በከተማ አስተዳደሩ የወሳኝ ኩነት ምዝገባን በበላይነት ይመራል፤ ያስተባብራል፤ ይመዘግባል፤ መመዝገቡንም ይቆጣጠራል ይከታተላል
  2. የነዋሪዎች መታወቂያና ሌሎችንም አገልግሎቶቸ ይሰጣል
  3. የክብር መዝገቦች ዝግጅትና ስርጭትን መረጃ አጠቃቀም ስርዒት አግባብ ካለው የፌደራል አካላት ጋር በመተባበር ይሰራል፤ ድጋፍ ይሰጣል፤ የክብር መዝገቦች ለሁሉም ወሳኝ ኩነት ምዝገባና መረጃ ደህንነት ጽ/ቤቶች መሰራጨታቸውን ያረጋግጣል፡፡
  4. የፈወሳኝ ኩነት ምዝገባ አስፈላጊነትን አስመልክቶ የተለያዩ ዘዴዎችን በመጠቀም ግንዛቤ ይፈጥራል ወይም እንዲፈጠር ያደርጋል፤
  5. የወሳኝ ኩነት ምዝገባ የጥራትና የሽፋን ደረጃ ለመገምገምና ለመቆጣጠር የሚያስችል ጥናት ያካሂዳል፣ ተግባራዊ ያደርጋል፤
  6. የወሳኝ ኩነት ምዝገባና ብሔራዊ መታወቂያ አዋጅ መሰረት የተሰበሰቡ መረጃዎችን አግነባብ ላለው ለፌደራል አካላት በወቅቱ ያስተላልፋል፤
  7. በቴክኖሎጂ በመታገዝ የዲሞክራሲና የባዮሜትሪክ የሰዎችን መረጃ ይመዘግባል፤ አገልግሎት ይሰጣል፤ ያስተዳደርራል፤ ይቆጣጠራል፤
  8. መንግስታዊ ተቋማት ማህበራትና የበጎ አድራጊዎች ድርጅቶች የሚደረገው የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ስርዓት የተሟላ እንዲሆን ተገቢውን ድጋፍ እንዲያደርጉ ያስተባብራል፤
  9. የድጂታል አገልግሎትን በከተማዋ በማሳለጥ የግለሰብ መረጃ መብትን በጠበቀ መልኩ የተመዝጋቢዎችን መረጃ እንደ አስፈላጊነቱ ለተቋማት ያጋራል፣ ደህንነቱንም ያስጠብቃል ወይም ይቆጣጠራል፤